News Archive

25 Feb 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሀገራቸን ዘመናዊ የዘካ አከፋፈል ሥርዓት በማስተዋወቅ ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለፀ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲቢኢ ኑር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኑሪ ሁሴን እንዳሉት፤ ባንካችን ከዘካ ክፍያና አሰባሰብ ሥርዓት ጋር በተያያዘ የከፋዮችን እና የተቀባዮችን ጊዜ፣ ጉልበትና ገንዘብ ብክነትን የሚያስቀር ፤ በዘመናዊ የባንክ አሠራር የተደገፈና ሚስጢራዊነቱን የጠበቀ፤ የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት ለደንበኞቹ በማቅረብ ፤በሀገራችን ፈር ቀዳጅ ነው::

25 Feb 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎትን በማሳደግ በአምስት ዘርፎች ሽልማት አገኘ፡፡

በመርሀ ግብሩ ላይ በመገኘት ባንኩ ያገኛቸውን ሽልማቶች የተቀበሉት የሲቢኢ ኑር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኑሪ ሁሴን እንዳሉት ከአምስቱ ሽልማቶች ሁለቱ የባንኩ የሥራ መሪዎች በግለሰብ ደረጃ ለዘርፉ ላደረጉት አስተዋፅኦ እውቅና የተሰጠባቸው ናቸው፡፡

04 Feb 2025

በስድስት ወራት ከ5.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ተከናወነ፡፡

በጀት ዓመቱ አጋማሽ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች በተከናወኑ እና በቁጥር ከ910 ሚሊዮን በላይ በሚደርሱ ግብይቶች ከ5.4 ትሪሊዮን ብር በላይ የሚደርስ የገንዘብ እንቅስቃሴ ተከናውኗል፡፡

04 Feb 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር አገልግሎትን በእያንዳንዱ ቤት ለማስገባት እየሠራ መሆኑ ተገለፀ፡፡

ባንኩ እስከበጀት ዓመቱ አጋማሽ ከሰጠው የ153.32 ቢሊዮን ብር ብድር ውስጥ 88 በመቶ የሚሆነው ለግሉ ሴክተር የተሰጠ ነው።