የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ኃላፊዎች ለ “ፅዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” መርሀ ግብር የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በመዲናችን የመፀዳጃ ቤቶችን ተደራሽ ለማድረግ ላስጀመሩት “ፅዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” መርሀ ግብር ብር 50,000 (ሀምሳ ሺ) የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ የድጋፍ ማሰባሰብ ዘመቻውን ተቀላቅለዋል፡፡ ሌሎች የባንኩ የሥራ ኃላፊዎችም የአቶ አቤን አርአያነት በመከተል የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን፣ ሁሉም የባንኩ ማህበረሰብ እና ኢትዮጵያውያን ለዚህ መልካም ዓላማ የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ አቶ አቤ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የድጋፍ ማሰባሰቢያ ሂሳብ ቁጥር፡ • የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር፡ 1000623230248 (Tsidu Ethiopia – Clean Ethiopia) • የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ ቁጥር፡ 0101211300016 https://172.31.6.10/cbeapi/uploads/final_c74872261a.pdf
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከተከሰተው የሲስተም ችግር ጋር በተገናኘ ያለአግባብ ተወስዶ ከነበረው ገንዘብ 95.4 በመቶ የሚሆነውን ማስመለስ ቻለ:: =========================== ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጠረ ችግር ምክንያት ብር 801,417,747.81 ያለአግባብ ተወስዶ እንደ ነበር የተገለጸ ሲሆን ከዚህም ገንዘብ ብር 764,567,820 ማስመለስ ተችሏል፡፡ ይህም መሰብሰብ ከነበረበት ገንዘብ ውስጥ 95.4 በመቶ የሚሸፍን ሲሆን ቀሪውን 4.6 በመቶ ብር 36,848,584 ገንዘቡን ተመላሽ ካላደረጉት ግለሰቦች የማስመለስ ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል፡፡
ባንኩ መጋቢት 7 ቀን 2016 ባጋጠመው የሲስተም ችግር ምክንያት ያለአግባብ የገንዘብ ልውውጥ እንደነበር ይታወቃል። በዚህም በርካታ ግለሰቦች በጥሬ ገንዘብ እና በዲጂታል የክፍያ አማራጮች የወሰዱትን የገንዘብ ልክ እየመለሱ ይገኛሉ። ሆኖም አንዳንድ ግለሰቦች የወሰዱትን ገንዘብ ወደ ቤቲንግ ተቋማት በማዛወራቸው መመለስ እንደተቸገሩ በጠቆሙን መሰረት ገንዘቡን ተመላሽ ማድረግ እንዲቻል ወደ ቤቲንግ ተቋማት የራሳችሁ ያልሆነውን ገንዘብ ያዘዋወራችሁ አቅራቢያችሁ በሚገኝ የባንካችን ቅርንጫፍ በመገኘት ለዚሁ የተዘጋጀውን ቅጽ በመሙላት እንድታመለክቱ እናሳስባለን። መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም
በባንኩ የሲስተም ማዘመኛ ሥራ ላይ የተፈጠረውን ክፍተት በመጠቀም መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. በሂሳብችሁ ከተቀመጠ ገንዘብ ውጭ በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ የወሰዳችሁ ግለሰቦች በፈቃደኝነት ሂሳባችሁ በሚገኝበት ቅርንጫፍ በአካል በመቅረብ ወይም ዲጂታል የክፍያ ዘዴን በመጠቀም ገንዘቡን እስከ ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ተመላሽ የምታደርጉበትን ዕድል ባንካችን ማመቻቸቱ ይታወቃል። በዚህ መሰረት 14,441 የሚሆኑ ግለሰቦች በተሰጠው ጊዜ ገደብ ተጠቅመው የወሰዱትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ እና በከፊል መልሰዋል፡፡ ሆኖም ከዚህ በታች ስማችሁ፣ የሂሳብ ቁጥራችሁ እና ሂሳባችሁ የሚገኝበት ቅርንጫፍ የተዘረዘረው 565 ግለሰቦች ባንኩ የሰጠውን ዕድል በመጠቀም ያላግባብ የወሰዳችሁትን ገንዘብ አለመመለሳችሁ ታውቋል። ባንኩ ቀደም ሲል ባስጠነቀቀው መሠረት ወደ ቀጣዩ ሕጋዊ እርምጃ ከማለፉ በፊት ገንዘቡን በአፋጣኝ እንድትመልሱ አንድ ተጨማሪ ዕድል የሰጣችሁ በመሆኑ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ድረስ ገንዘቡን በምትመልሱት ላይ በባንኩ በኩል ቀጣይ ሕጋዊ እርምጃ እንደማይኖር ያረጋግጣል። ነገር ግን እስከተጠቀሰው ቀን ገንዘቡን የማትመልሱ ካላችሁ ግን የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዘዴዎችን በመጠቀም ሙሉ ስማችሁን፣ ፎቷችሁን፣ በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራችሁን ጠቅሰን ለሚመለከታቸው የሕግ አካላትና ተቋማት በማሳወቅ ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግ ፤ እንዲሁም ከሕግ አካላትና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር ቀጣይ የወንጀል፣ የፍትሐ ብሔርና የአስተዳደር ሕጋዊ እርምጃዎች እንደሚወሰድባችሁ ለመጨረሻ ጊዜ እናሳስባለን። መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም. የስም ዝርዝሩን ለማየት የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ፡ https://combanketh.et/cbeapi/uploads/New_No_repayment_alphabet_e1dcbe678e.pdf
በባንኩ የሲስተም ማዘመኛ ሥራ ላይ የተፈጠረውን ክፍተት በመጠቀም መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. በሂሳብችሁ ከተቀመጠ ገንዘብ ውጭ በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ የወሰዳችሁ ግለሰቦች በፈቃደኝነት ሂሳባችሁ በሚገኝበት ቅርንጫፍ በአካል በመቅረብ ወይም ዲጂታል የክፍያ ዘዴን በመጠቀም ገንዘቡን እስከ ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ተመላሽ የምታደርጉበትን ዕድል ባንካችን ማመቻቸቱ ይታወቃል። በዚህ መሰረት 9281 የሚሆኑ ግለሰቦች በተሰጠው ጊዜ ገደብ ተጠቅመው የወሰዱትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ መልሰዋል፡፡ ሆኖም ከዚህ በታች ስማችሁ፣ የሂሳብ ቁጥራችሁ እና ሂሳባችሁ የሚገኝበት ቅርንጫፍ የተዘረዘረው 5166 ግለሰቦች ባንኩ የሰጠውን ዕድል በመጠቀም ያላግባብ ከወሰዳችሁትን ገንዘብ በከፊል ተመላሽ ያደረጋችሁ ቢሆንም ይህ ማስታወቂያ ይፋ እስከሆነበት ዕለት ድረስ ቀሪውን ገንዘብ አልመለሳችሁም፡፡ ባንኩ ቀደም ሲል ባስጠነቀቀው መሠረት ወደ ቀጣዩ ሕጋዊ እርምጃ ከማለፉ በፊት ቀሪውን ገንዘብ እንድትመልሱ አንድ ተጨማሪ ዕድል የሰጣችሁ በመሆኑ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ድረስ ገንዘቡን በምትመልሱት ላይ በባንኩ በኩል ቀጣይ ሕጋዊ እርምጃ እንደማይኖር ያረጋግጣል። ነገር ግን እስከተጠቀሰው ቀን ገንዘቡን የማትመልሱ ካላችሁ ግን የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዘዴዎችን በመጠቀም ሙሉ ስማችሁን፣ ፎቷችሁን፣ በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራችሁን ጠቅሰን ለሚመለከታቸው የሕግ አካላትና ተቋማት በማሳወቅ ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግ ፤ እንዲሁም ከሕግ አካላትና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር ቀጣይ የወንጀል፣ የፍትሐ ብሔርና የአስተዳደር ሕጋዊ እርምጃዎች እንደሚወሰድባችሁ ለመጨረሻ ጊዜ እናሳስባለን። መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም. የስም ዝርዝሩን ለማየት የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ፡ https://ow.ly/iYtO50R2WrV
CBE Noor is one of the full-fledged interest free banking services. Designed to comply with the central tenets of Sharia (or Islamic law) of doing business.
The core processes of the bank entrusted with the task of international banking services. The services are now provided at all branches of the bank with a single contact point of customer service relationship officers assigned for this purpose only.
Delivering banking services through high level of process automated machines and web-based. It provides easy, convenient, flexible and secure banking services for CBE customers using their digital cards, mobile phone, or internet accesses.
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በመዲናችን የመፀዳጃ ቤቶችን ተደራሽ ለማድረግ ላስጀመሩት “ፅዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” መርሀ ግብር ብር 50,000 (ሀምሳ ሺ) የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ የድጋፍ ማሰባሰብ ዘመቻውን ተቀላቅለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ ባንኩ ከሰሞኑ ገጥሞት ከነበረ ችግር ጋር በተያያዘ ለባንኩ ድጋፍ ላደረጉ አካለት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ፕሮፌሰር መሐመድ አብዱ እንዳሉት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሀገር የልማት እንቅስቃሴ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ ያለ ባንክ ነው፡፡ባንኩ በሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ውስጥ የሚጠብቀበትን እየተወጣ እንዲቀጥል እና በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን ያስቀመጠውን ግብ ለማሳካት ይረዳው ዘንድ ደግሞ የባለድርሻ አካላት የፖሊሲን ጨምሮ ተገቢውን ድጋፍ ሊያደርጉለት እንደሚገባ ዋና ሰብሳቢው አሳስበው፣ ቋሚ ኮሚቴው አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል፡፡
በዛሬው እለት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንደገለፁት ባንኩ መጋቢት 6፣ 2016 ዓ.ም ሌሊት በተፈጠረ ችግር ምክንያት አላግባብ ከተወሰደበት 801,417,747.81 ብር ውስጥ 622.9 ሚሊዮን ብር (78 በመቶ) እስካሁን የተመለሰ ሲሆን ብር 168,609,283.7 ለመመለስ ቃል ተገብቷል፡፡ አቶ አቤ አላግባብ በ567 ግለሰቦች የተወሰደውን ቀሪ ብር 9,838,329.12 ለማስመለሰ ባንኩ ወደቀጣይ እርምጃዎች እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ መጋቢት 6፣ 2016 ዓ.ም ሌሊት በተፈጠረ ችግር ምክንያት 801,417,747.81 ብር ያላግባብ ተወስዶ እንደነበር ባንኩ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ያሳወቀ ሲሆን፣ 622.9 ሚሊዮን ብር ማስመለስ መቻሉ ተገልጿል፡፡ ከባንኩ አላግባብ የተወሰደውን ገንዘብ ለማስመለሰ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ለህብረተሰቡ ለማሳወቅ በተዘጋጀው በዚህ ጋዜጣዊ መግለጫ የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንደገለፁት ችግሩ በተከሰተበት ቀን ከምሽቱ 3፡38 ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 8፡45 ድረስ በ25,761 ሂሳቦች አማካኝነት 238‚293 ህገወጥ ግብይቶች ተከናውነዋል፡፡
ሰሞኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካጋጠመው የሲስተም ችግር ጋር ተያይዞ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ የወሰዱና ያልተገባ የገንዘብ እንቅስቃሴ ካከናወኑ ግለሰቦች መካከል ብዙዎች የተደረገላቸውን ጥሪ ኣክብረው የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ወደ ባንኩ ቅርንጫፎች እየቀረቡ እየመለሱ በመሆኑ ከስህተታቸው የመመለስ በጎ ምላሽነቱን እናደንቃለን። እስካሁን ቀርበው ገንዘቡን ተመላሽ ያላደረጉ ግለሰቦችም እስከመጪው ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ የባንካችን ቅርንጫፍ በመቅረብ ተመላሽ እንዲያደርጉ ባንካችን የመጨረሻ ጥሪ ያቀርባል፡፡
Branchs
Customers
Partners
Transactions per Month