የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲስ መስጠት የጀመራቸው የቁጠባ ሂሳብ አገልግሎቶች 1. እድሜያቸው ከ55 ዓመት በላይ የሆኑ የእድሜ ባለፀጎች የሚከፍቱት ‘ጋሻ የቁጠባ ሂሳብ’ (በሲቢኢ ኑር አገልግሎት ‘ቀዲም ሙዳራባህ የቁጠባ ሂሳብ‘ እና ‘ቀዲም ወዲዓህ የቁጠባ ሂሳብ‘)፣ 2. ደንበኞች ከውጭ ሀገራት የሚላክላቸውን ገንዘብ በባንኩ በመቀበል፣ ወይም በባንኩ የሚመነዝሩትን የውጭ ሀገር ገንዘብ የሚያስቀምጡበት ‘የውጭ ሐዋላ የቁጠባ ሂሳብ‘ ፣ 3. ደንበኞች ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ጉዞ ወጪ መሸፈኛ ገንዘብ የሚቆጥቡበት ‘ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ‘ (በሲቢኢ ኑር አገልግሎት ‘ሲቢኢ ሪህላ ወዲዓህ የቁጠባ ሂሳብ‘ እና ‘ሲቢኢ ሪሕላ ሙዳራባህ የቁጠባ ሂሳብ‘) ናቸው፡፡ አገልግሎቶቹ ከመደበኛው ቁጠባ ሂሳብ ተጨማሪ ጥቅሞች እንዲኖራቸው ተደርገው የተዘጋጁ ናቸው፡፡ ደንበኞች የቁጠባ ሂሳቦቹን በመክፈት ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን ማግኘት ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሰረት ከ 15 ዓመት በላይ ሳይንቀሳቀሱ የቆዩ ሒሳቦችን በባንኩ ድረ ገጽ ላይ ለሕዝብ እንዲታይ በተጠየቀው መሰረት በዚህ ማስፈንጠሪያ ማየት የሚቻል መሆኑን እንጠቁማለን። https://combanketh.et/en/downloads
በአፍሪካ ሕብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ድርድር የሀገራችንንና ህዝቦቿን ጥቅም ባስጠበቀና ዘላቂ ሰላም በሚያመጣ መልኩ ተጠናቋል። በዚህም የሕዝባችንን የሰላም ወዳድነት እንዲሁም ሀገራችን ለአፍሪካ ሕብረት የሰላም መርሆዎች ያላትን ታማኝነት በድጋሚ ማስመስከር ተችሏል። በዚህ ስኬት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ማኔጅመንትና ሠራተኞች የተሰማንን ደስታ እየገለጽን ሰላማችንን ለመመለስ ዋጋ ለከፈሉ ሁሉ ምስጋና እናቀርባለን። በዚህ አጋጣሚ በግጭት አካባቢዎች ተቋርጦ የከረመውን የባንክ አገልግሎት በፍጥነት ለማስቀጠል በከፍተኛ ርብርብ እንደምንሰራ ለክቡራን ደንበኞቻችን ማሳወቅ እንፈልጋለን። በድጋሚ እንኳን ደስ ያለን!! ጥቅምት 24, 2015
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ለ10 አመት የሚቆይ የ200 ሚሊዮን ብር የስፖንሰርሺፕ ስምምነት በሸራተን አዲስ ሆቴል ተፈራረሙ፡፡ ========================= ሰኔ 16 ቀን 2014 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል የተፈረመው ስምምነት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነቱን ለማሳደግ የጀመረውን የዘመናዊ ስቱዲዮ ግንባታ በአጋርነት ለመሥራት የሚያስችል ነው፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አዲሱ የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ መርቀዋል።
CBE Noor is one of the full-fledged interest free banking services. Designed to comply with the central tenets of Sharia (or Islamic law) of doing business.
The core processes of the bank entrusted with the task of international banking services. The services are now provided at all branches of the bank with a single contact point of customer service relationship officers assigned for this purpose only.
Delivering banking services through high level of process automated machines and web-based. It provides easy, convenient, flexible and secure banking services for CBE customers using their digital cards, mobile phone, or internet accesses.
ሰኔ 3 ቀን 2015 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በተካሄደ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ በአባልነት ሲያገለገሉ የቆዩት አቶ ማሞ እስመለዓለም ምህረቱ፣ ዶ/ር አብርሃም በላይ እና አቶ ነብዩ ሳሙኤል የአገልግሎት ዘመናቸውን አጠናቀው የክብር ሽኝት ተደርጎላቸዋል፡፡ በዕለቱ ተሰናባች የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን ለተኩት ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ፣ ወ/ሮ ትዕግስት ሀሚድ እና አቶ ወንድምአገኘው ነገራ እንዲሁ የክብር አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዋናው መስሪያ ቤት በተዘጋጀ መርሀ ግብር የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ለበይክ ሙዳራባህ የተሰኘ አዲስ የሲቢኢ ኑር የቁጠባ ሒሳብ አገልግሎት ያስተዋወቀ ሲሆን፣ 3ኛውን ዙር "ሐጅ ለሁሉም" የንቅናቄ መርሃ ግብርም በይፋ አስጀምሯል።
በኢትዮጵያ አስተማማኝ ዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያግዝ በታለመው በዚህ የልምድ ልውውጥ ላይ በአቶ አቤ ሳኖ የሚመራ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ አመራር አባላት ልኡክ በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡
በሃገራችን ሁለንተናዊ የልማት እና የዕድገት ጉዞ ውስጥ ቀዳሚ ሚና በመጫወት ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም በአጋርነት፤ ዜጎች ዲጂታል የብድር እና የቁጠባ አገልግሎቶችን በቴሌብር እንዲያገኙ የሚያስችል የሞባይል የፋይናንስ አገልግሎት ሰኔ 20 ቀን 2015 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በተዘጋጀ መርሐ-ግብር በይፋ አስጀምረዋል፡፡ ሁለቱ ተቋማት በአጋርነት ያስጀመሩት አገልግሎት የባንክ እና የፋይናንስ አገልግሎትን ተደራሽነት እና ተጠቃሚነት ለማረጋግጥ የሚያስችል፣ ዜጎች ባሉበት ሆነው ፈጣን እና ቀላል በሆነ አማራጭ የፋይናንስ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡
ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ እና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራአስኪያጅ አኑዋር ሱሳ ናቸው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ በስምምነቱ ወቅት እንደተናገሩት ባንኩ በቴሌኮም ዘርፍ አለም አቀፍ ልምድ ካለው ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት እድል በማግኘቱ መደሰታቸውን በመግለፅ ሁለቱ ትላልቅ ድርጅቶች በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ በመስራት በጋራ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያረጋግጡ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስትራቴጂክ አጋርነት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አዘጋጅነት በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበረው ሶስተኛው የሳይበር ደህንነት ወር መርሃ ግብር ጥቅምት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ተጀምሯል፡፡
Branchs
Customers
Partners
Transactions per Month